ጎሽ የጤና ትምህርትና ምክር በአማርኛ
አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር ገበየሁ ተፈሪ
Community health
education in Amharic
ስለ አልኮልና እርግዝና አጠቃላይ ምክሮች
በእርግዝና ጊዜ ጤናማ የሚባል የአልኮሆል መጠን የለም
በእርግዝና ጊዜ አልኮሆል መጠጣት ላይ የሚያስከትለው አደጋ
እንደሚታወቀው፣ ፅንሱ የሚያድገው በእትብቱ በኩል የእናትየዋን ደም በመቀበል ነው፡፡ ሰለዚህ እናትየዋ አልኮሆል በምትጠጣበት ጊዜ በደሟ ውስጥ የሚዘዋወረው አልኮሆል በቀጥታ ወደ ፅንሱ ይሄዳል፡፡ ስለዚህ አልኮሆል ፅንስ መጨናገፍን፣ ሕይወት የሌለው ልጅ መወለድን በማስከተል የሚታወቅ ሲሆን በተጨማሪ
ሕፃኑ ለአልኮሆል በመጋለጡ ምክንያት፣ ለዕድሜ ልክ የሚዘልቁ በሰውነት አካል፣ በአእምሮና በባህሪ ላይ ችግሮች ያስከትላል፡፡ እነዚህ ችግሮች በእንድ ላይ፣ በእንግሊዝኛ፣ ፊታል አልኮሆል ስፔክተርም ዲሶርደር ተብሎ ይታወቃል (fetal alcohol spectrum disorders (FASDs). ለመግባባት እንዲመች ምህፃረ ቃሉን ማለትም FASDs የሚለውን መጠቀም ይቻላል፡፡
በዝርዝር ሲታይ FASDs ያለባቸው ህፃናት የሚከተሉት ችግሮች ይታዩባቸዋል
ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች በአብዛኛው በአንድ ላይ ሊታዩ ይችላሉ፡፡ ሆኖም ከላይ እንደተዘረዘረው በየጊዜው የሚታወቁት ለምሳሌ ትምህርት ላይ ደካማ መሆን ቆየት ብለው ነው የሚታወቁት፡፡ ከዚህ በላይ ሌላ ምን አደጋ አለ? ከላይ የተዘረዘሩት ችግሮች ያለበት ህፃን መውለድስ ይበጃል ወይ? ይህ ችግር ሁሉም አልኮሆል የጠጡ ነብሰጡሮች ላይ ላይከሰት ይችል ይሆናል፡፡ ነገር ግን ማን ላይ ሊከሰት እንደሚችል የሚጠቁም ምልክት የለም፡፡ ስለዚህ ሊከሰቱ በሚችሉት በነዚህ ችግሮች ምክንያት፣ አይደለም በእርግዝና ጊዜ፣ ለእርግዝና አየተዘጋጁ ከሆነ እንዳውም ያለመከላከያ ግብረ ሥጋ ግንኙነት የምታደርግ ሴት ከአልኮሆል መቆጠብ አለባት ነው ምክሩ፡፡ ምክንያቱም አብዛኘው እርግዝና ሳይታሰብና ሳይታወቅ ነው የሚጀመረው፤ እናም ሴቶች ነብሰ ጡር መሆናቸውን ሳያውቁ አልኮሆል በመጠጣት ፅንሱን ሊያጋልጥ ስለሚችሉ ነው፡፡ ነብሰ ጡር መሆናቸውን ካወቁ በኋላም ወዲያውኑ ማቆም በጣም ይረዳል፡፡ የሚወለደው ልጅ የጋራ እንደመሆኑ አባቶችም ቢሆን በዚህ ነገር መተባበር ያስፈልጋል፡፡
እንደሞጋቾቹ አሸብር ሚስትን እየጎተቱ መጠጥ መጋበዙ ግብዝነት ነው፡፡ የሞጋቾች ድራማ ፀሀፊዎችም ቢሆን መድረካቸውን ተጠቅመው መልክቱን ቢያስተላልፉ ጥሩ ነው፡፡
ባካችሁ አካፍሉ፡፡ ማንኛውም ሰው ማወቅ የሚገባው ነገር ነው፡፡