​ጎሽ የጤና ትምህርትና ምክር በአማርኛ


አዘጋጅና አቅራቢ 
ዶ/ር ገበየሁ ተፈሪ

Community health 

education in Amharic 

Back cover

ቅድመ አድዋ፣ በአድዋ ከዛም በኋላ የተደረገውን የአውሮፓ ተንኮል፣ የምኒልክ ቤተ መንግሥትን የብልጠት አካሄድ በዝርዝር፣ ከዚህ በፊት ለንባባ ባልቀረቡና ሊገኙ በማይችሉ መረጃዎቸ አስደግፎ የቀረበ ፅሁፍ ነው፡፡
ግብፅም ቢሆን፣ ኢትዮጵያ የደከመች ሲመስላት በኢትዮጵያ ላይ የወሰደችውን ርምጃ፣ የአሁን የአባይ ችግር ጥንስስ የተጀመረበትን ሁኔታ በዝርዝር የሚያቀርብ ፅሁፍ ነው፡፡


"ኢንግላንድ ግብፅን ሰለያዘች፣ የግብፅን የህይወት ምንጭና የውሀውን ተፋሰስ ለመቆጣጠር መመኘት አለባት፡፡ እነዚህ ደግሞ በኢትዮጵያ ተራራማ ቦታ ነው የሚገኙት፡፡" 

ከመጽሐፉ የተወሰደ


ከፖለቲካ አቀንቃኝ አስከ ዲፕሎማት ብሎም ሁሉም የሀገሪቱ ዜጋና ትውልድ ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ ነው፡፡
ይህንን የሀገሪቱ ወሳኝ ታሪክ ማወቅ የግድም ነው፡፡ ተርጓሚው፣ ኢትዮጵያ እንዴት ተረፈች? በማለት ንዑስ ርዕስ የሠጠው ይህ መጽሐፍ፣ ባነበቡት ሰዎች ደግሞ፣ እንዴት ትተርፋለች? የሚል ጥያቄ አስነስቷል፡፡ 

ሰዎችም በተለያየ መልክ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡
ወደፊት ሰለመጽሐፉ የተሠጡ አሰተያየቶችን በዘህ ገፅ እናሰፍራለን፡፡
ባጠቃላይ ግን፣ ማንም ኢትዮጵያዊ ሊያወቀውና ወይም ሊያነበው የሚገባ ጽሁፍ መሆኑን ሁሉም ያነበቡ ሰዎች በምስክርነት የሚገልፁት ነገር ነው፡፡

Health and History

ኢትዮጵያ  በአውሮፓ  ዲፕሎማሲ እንዴት  ተረፈች በሚል ርዕሰ  በቅርቡ በዶክተር  ገበየሁ  ተፈሪ ተተርጉሞ  የተረቀውና ገበያ ላይ ስለዋለው መጽሐፍ  በበኩሌ መጽሐፉን  ከአነበብኩ በኋላ ጊዜውን ገንዘቡና እውቀቱን በመጠቀም  ስሚወዳት ኢትዮጵያ  ለማዋል  ለአደረገው ከክፍተኛ ጥረት ልባዊ አድናቆቴንና ምስጋናዬን  መግለጽ እወዳለሁ ::
በመቀጠል ይህ በመረጃ የተደገፈ  መጽሐፍ  ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ  ከአለችበት ውጥንቅጥ  ለመውጣት እንደመፍትሔ  በድጋፍ መረጃነት እንዲያገለግል  ለውጭጉዳይ ሚንስትር  ለትምህርት  ሚንስትርና ለሌሎችም  የሚመለከትቸው አካላት  ቢላክ ጥሩ  ነው የሚል  ሀሳብ  ለመሰንዘር  ነዉ ።
ይህ  መጽሐፍ  ኃያላኑ  የአውሮፓ  አገሮች  አፍሪቃን በቅኝ ግዛት ለመቀራመት በ1885 በርሊን  ኮንፈረንስ  ተነስተው  እሽቅድምድም  ይዘው  አንደነበር  በማብራራት  ሩሲያ  ጀርመን  ብሪታኒያ  ጣሊያንና ፈረንሳይ  የነበራቸውን  ፍላጎት ሁሉ  ተቋቁማና ተርፋ  ዛሬ  ላይ መድረሷን  ያስረዳል ። 
ከዚህ የማስቀጠል  የአሁኑ  ትውልድ  ተሸክሞ  ይሆናል 

Back cover